Psalms 61

የግዞተኛ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ጩኸቴን ስማ፤
ጸሎቴንም አድምጥ።

2ልቤ በዛለ ጊዜ፣
ከምድር ዳርቻ ወደ አንተ እጣራለሁ፤
ከእኔ ይልቅ ከፍ ወዳለው ዐለት ምራኝ።
3አንተ መጠጊያዬ፣
ከጠላትም የምተገንብህ ጽኑ ግንብ ሆነኸኛልና።

4በድንኳንህ ለዘላለም ልኑር፤
በክንፎችህም ጥላ ልከለል። ሴላ
5አምላክ ሆይ፤ ስእለቴን ሰምተሃልና፤
ስምህን የሚፈሩትንም ሰዎች ርስት ለእኔ ሰጠህ።

6የንጉሡን ዕድሜ አርዝምለት፤
ዘመኑንም እስከ ብዙ ትውልድ ጨምርለት፤
7በእግዚአብሔር ፊት ለዘላለም ይንገሥ፤
ይጠብቁት ዘንድ ምሕረትህንና ታማኝነትህን አዘጋጅለት።

8ስለዚህ ለስምህ ዘወትር ውዳሴ አቀርባለሁ፤
ስእለቴንም በየጊዜው እፈጽማለሁ።
Copyright information for AmhNASV